Selected:

The Revolution and My Reminiscence

$44.95

The Revolution and My Reminiscence

አብዮቱና ትዝታዬ

ISBN Code : 978-1-59907-108-4
Author: Fisseha Desta
Language: Amharic
Pages number: 598
Format: Paperback
Publication date: 09/12/2015

$44.95

Description

የኢትዮጵያ አብዮት ሰፊ፣ ፈጣንና ውስብስብ የነበረ ቢሆንም በግሌ ተካፋይ የነበርኩበትን፣ በዓይኔ ያየሁትንና በማስረጃ ያረጋገጥኳቸውን እውነታዎችን በተቻለ መጠን ከወገናዊነት በፀዳ መልኩ በዚህ መጽሐፍ ለማቅረብ ሞክሬአለሁ። የኔ ምኞትና ፍላጎት እኩልነት፣ የሕግ የበላይነትና ዲሞክራሲ የሰፈነባት፣ አንድነቷና ልዑላዊነቷ የተጠበቀና የበለጸገች አንዲት ኢትዮጵያን ማየት ነው። ዓላማ በመንደር ልጅነት፣ በጎሳና በዘር የሚለወጥ አይደለም። በዚያ የአብዮት ወቅት የተጋረጠብኝን ሴራና ተንኮል በመቋቋም፤ የገባሁትን ቃል ኪዳንና መሃላ ጠብቄ በንጹህ ህሊናና ቅንነት ሃገሬንና ሕዝቤን አገልግያለሁ። ደርግ በወሰዳቸው በጎ እርምጃዎች እንደምደሰት ሁሉ፤ በማወቅ፣ በድፍረት፣ ባለማወቅና በስህተት ለተፈጸሙት ደግሞ፤ ሙሉ ሃላፊነትን በመውሰድ፤ በበኩሌ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ።

የሰው ልጅ በተለያየ ምክንያት ለተለያየ ተፅእኖ መውደቁ ስለማይቀር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ለራስ በማድላት ፍፁም ከወገናዊነት የፀዳ አይሆንም። እኔም ሙሉ በሙሉ ከወገናዊነት ውጭ ነኝ ብዬ ስለማላምን አንባብያን ይህንን በቅን ልቦና እንዲወስዱልኝ እጠይቃለሁ። ከሰው ስህተት አይጠፋምና መጽሐፉን በሚገባ አንብበው በጭፍን ሳይሆን በገምቢ መልኩ የሚሰጡትን ማንኛውንም አስተያየትና ሂስ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ።

Close Menu
×
×

Cart